ለ አእምሮ / Le'Aimero ለ አእምሮ የጥር 2006 / January 2014/ እትም፣ ቅጽ 2 ቁጥር 6 | Page 43

ደርግ /ኢሠፓ የመደብ ትግሉን አራማጅ ሠፈር -እየፈጀና እየገደለ ለብቻው ይህን ቦታ ይይዛል። ነጻ-አውጪዎቹ „ የብሔር ትግሉን እሰከ መገንጠል“ ይዘው ያቺን አገር – ዛሬ መለስ ብለን ስንመለከተው የትም አገር በአልሰራ ዕውቀትና ጥበብ ትምህርት- ሁለቱ ወገኖች ተነስተው ያን አካባቢ እንዳልነበር አድርገው እነሱ -የቫይመርን ታሪክ ተመልከትበይገባኛል ጥያቄ አተረማምሰዋል። የሚደንቀው ከዚህ ሁሉ ትርምስና ሕይወት መጥፋት በሁዋላ ደግሞ አሁንም ቢሆን እነሱው ናቸው መጽሐፍ እየጻፉ ወረቀት እያወጡ የፖለቲካ ሜዳውን ለብቻቸው የያዙት! ሌኒን እና ስታሊን በጀርመን ንጉሥ ዕርዳታ ነው ሥልጣን ላይ የወጡት። አብዮት ካለውጭ ዕርዳታ የማይሳካ ይመስል ደርግ በሶቭየት እሱን የተኩት „ነጻ-አውጪዎቹ“ ደግሞ በጎረቤት አገሮችና በምዕራቡ ዓለም በእነሱ ብርታት ሥልጣን ላይ ወጥተዋል። ደርግና እነ ኮነሬል ምንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ሥልጣን ላይ ለ17 አመታት የቆዩት በሶቪየት ገንዘብና በእነሱ መሣሪያ፣ በምሥራቅ ጀርመን የስለላ ድርጅት ድጋፍና በሁዋላ በመጣችው ኪዩባ ነው። ደርግ በተራው-በሩ አሁን ለማንም ክፍት ነው- በውጭ ኃይሎች ትብብር ከሥልጣኑ ይወርዳል። መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም በእነሱ ምክር፣ ንዋይና ድጋፍ አገሪቱን ለቆ ይወጣል። በብሔር ትግል ስም ሥልጣኑን የተረከቡት ኢትዮጵያን ለሁለት ከፍለው የያዙት ሕዝባዊ ወያኔና ሻቢያ ለአጭር ጊዜ ኦነግ -ሦስቱም ድርጅቶች ተመካክረው -ዩጎዚላቪያ እየተገነጣጠለች ሶቪየት ኅብረት እንደዚሁ እየተፈረካከሰች እያዩ፣ – ሕገ- መንግሥቱ ላይ „…እሰከ መገንጠል „ የሚለውን የስታሊን መፍትሔ ለኢትዮጵያ ይተልማሉ። ምሳሌ ሲሰጡ ሌኒን እና ስታሊን አንዴ የሰጡትን የባልና ሚስት የፍች ወረቀት ጉዳይ መልሰው መላልሰው እነሱ ያነሳሉ። 43