ለ አእምሮ / Le'Aimero ለ አእምሮ ሚያዝያ 2006 / April 2014 / እትም፣ ቅጽ 2 ቁጥር 08 | Page 43
ለግብጽ የጦር አይሮፕላኖች ማረፊያ መሬት -ያውም የኢትዮጵያ ድንበር
አጠገብ- ሰጠች“ የሚለውን አረፍተ ነገር ይዞልን ብቅ ብሎአል።
የአባይ ወንዝ የሚነሳባቸውና የሚያቋርጣቸው አገሮች ብዙ ናቸው።
ብሩንዲና ኬንያ ሩዋንዳና ሁለቱ ሱዳኖች ታንዛኒያና ኡጋንዳ በትንሴም
ቢሆን ከኢትዮጵያ የተገነጠለቺው ኤርትራና እራሱዋ ትልቁዋ የጥቁር
አባይ ወንዝ አቅራቢ ኢትዮጵያ እነዚህ ሁሉ ናቸው።
ግብጽ በጦር አይሮፕላኖቹዋ
ተነሳታ ልትደባደብና ልትማታ
የፈለገችው አገር ሌሎቹን
ሳይሆን ኢትዮጵያን ያውም
ድፍን ኢትዮጵያን ሳይሆን
ከሱዳን የማይርቀውን የወሃ
ግድብ ነው። ለግብጽ የጦር
አይሮፕላን ማረፊያ ሱዳን ሰጠች
የተባለውም መሬት ከዚያ ቦታ
የማይርቅ ነው።
ሕጉ- የዓለም አቀፍ ሕጉ
የአባይን
ወሃ
ለመጠቀም
የሚፈቅደው
ለማን
ነው?
ለግብጽ ወይስ ለኢትዮጵያ?
መነጋገር የለም እንጂ መነጋገር
ቢኖር መመካከር የለም እንጅ መመካከር ቢኖር እዚህ ጀርመን አገር
ሰው የሚጠቀመውና የሚገለገልበት ወሃ ቢያንስ ከአምስት ጊዜ በላይ
ተመልሶና ተጣርቶ በቧንቧ የሚመጣ ወሃ ነው።
ወሃ “ቆሻሻ”ተብሎ አንዴ የተጠቀምነው ወሃ ቢሆን እንኳን አይደፋም።
ወሃን እንዲጣራና ተመልሶ እንደገና እንድንጠቀምበት ንጹህ ወሃው
በቧንቧ እቤት ድረስ ሰተት ብሎ እንደመጣው ሁሉ በተማሳሳይ ዘዴ
ተመልሶ በቧንቧ ያ ወሃ አንዲት ጠብታ ደጃፍ መሬት ላይ ሳትወድቅና
ሳትደፋ ወደ ጥራት ገንዳው በቶቦ እዚያ እንዲደርስ ይላካል።
~ 43 ~